- አጭር የታሪክ ማስታወሻ
ተወደደም
ተጠላም፤ እስካኹን ባገራችን ሰፍኖ ያለው “ገዡ መንፈስ” የኢትዮጵያዊነት መንፈስ ነው። የተቀረው አንድም ተፎካካሪ ወይም አኩራፊ
አለያም ተፃራሪ ነው፤ ኢትዮጵያዊነትን።
ናሁኬ ፈለሰት በረከተ እግዚአብሔር ኀበ ቤተ ዳዊት... ወእምዘርዐ ዚኣሁ አንሥአ ለነ እግዚአብሔር ቀርነ መድኀኒትነ። ወዓዲ ኢቦአ ውስተ አዕጻዳቲሆሙ ለነገሥተ ገሊላ። ኢኀረያ ለወለተ ሄሮድስ። ወለተ ነዳያን ኀረየ እምወለተ ዐበይቶሙ ለነገሥተ ይሁዳ። እንዘ እግዚአብሔር ውእቱ ውስተ ማሕፀነ ብእሲት ኀደረ።...
እነሆ የእግዚአብሔር በረከት ወደዳዊት ቤት ገባች... ከዘሩም እግዚአብሔር የድኅነታችንን ቀርን [ሊያድነን ሥልጣን ያለው ክርስቶስን] አስነሣልን።